ኢትዮጵያ እና ኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቢል ) በወታደራዊ መስኮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

ሁለቱ ሃገራት በመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ የሁለትዮሽ ውይይት ካካሄዱ በኋላ በጋራ ለመስራት በሚቻልባቸው ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ እና የኮንጎ ሪፐብሊክ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በይፋ የተመሰረተው ኮንጎ ነፃነቷን ካገኘች በኋላ ነው።

ኢትዮጵያ በወቅቱ በአፍሪካ የነፃነት ንቅናቄ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራት በመሆኗ፣ ኮንጎ ሪፐብሊክ ነፃነቷን ባገኘችበት በ1960ዎቹ መጀመሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን በይፋ መሥርታለች።

ግንኙነቱ በዋናነት የተጀመረው በዓለም አቀፍ መድረኮች በተለይም በአዲስ አበባ በተመሠረተው በቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) እና በአሁኑ  የአፍሪካ ኅብረት (AU) ማዕቀፍ ውስጥ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሃመድ ኢትዮጵያና ኮንጎ ሪፐብሊክ ረጅም አመታትን ያስቆጠረ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልፀዋል ።

ኢንጅነር አይሻ ከኮንጎ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስትር ጋር በዋናነት በወታደራዊ ኢንዱስትሪ ውጤቶች  ፣ በጦር መሳሪያ ጥገና ፣ በትምህርትና ስልጠና እና በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን ገልፀዋል።

ስምምነቱ የሁለቱን ሃገራት ወታደራዊ አቅም በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል እድል ይፈጥራል ብለዋል።
አሁን ያለንበት አለም በትብብር መስራትን ይጠይቃል ያሉት ክብርት ኢንጅነር አይሻ ድንበር ዘለልና ሽብርተኝነት የመሳሰሉ ቀጠናዊ ችግሮችን በጋራ  ለመከላከልም ከፍ ያለ በጎ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

ከሌሎች አገራት ጋር የሚኖረን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ክብርት ሚኒስትሯ ተናግረዋል።

የኮንጎ ብራዛቢል መከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር  ቻርለስ ሪቻርድ ሞንጆ በበኩላቸው ስምምነቱ የሁለቱን ሃገራት ሰላምና ደህንነት የበለጠ ለማጎልበት የጎላ ፋይዳ እንዳለው ተናግረው የመግባቢያ ስምምነቱን ወደ ተግበራ ለመቀየር  በቅርቡ ወደ ተጨባጭ ስራ እንገባለን  ብለዋል።

የኮንጎ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ቻርለስ ሪቻርድ ሞንጆ ለክብርት ኢንጅነር አይሻ መሃመድድ ኮንጎ ብራዛቢልን እንዲጎበኙም  ግብዣ አቅርበውላቸዋል ።

የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሃመድ ለኮንጎ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር የተለያዩ ስጦታዎችን ያበረከቱ ሲሆን በተመሳሳይ የኮንጎ መከላከያ ሚኒስትር ቻርለስ ሪቻርድ ሞንጆ ያዘጋጇቸውን ስጦታዎች ለኢንጅነር አይሻ መሃመድ ሰጥተዋል።

ዘጋቢ በላቸው ክንዴ
ፎቶግራፍ ገነት አወቀ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።