የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ልዩ ስሙ አስጎሪ በተባለ ቦታ ህገ-ወጥ መሳሪያ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
በስፍራው የተሰማራው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል ክፍለጦር ባደረገው የተቀናጀ ክትትል ህገ ወጥ መሳሪያው በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፍቃዱ ጥላሁን ገልፀዋል፡፡
ክፍሉ በአካባቢው ከተሰማራበት ጊዜ ጀምሮ በቀጠናው ሰላም ለማስፈን የሽብር ቡድኖችን እየተከታተለ በመደምሰስ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሰላም ማስፈኑን ገልፀው የሽብር ቡድኑ ለጥፋት ተልዕኮ የሚጠቀምበትን የህገ-ወጥ መሳሪያ ዝውውር እና ንግድ ከምንጩ ለማድረቅ በአቅራቢዎችና በተቀባይ የጠላት ህዋሶች ላይ የሚደርገው ቁጥጥር የተሳካ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል፡፡
ሰሞኑን በተደረገው ክትትል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችና ሽጉጥ፣ የብሬንና ልዩ ልዩ ተተኳሾች መያዛቸውንና ህገ-ወጥ መሳሪያ የሚገበያዩበትን ገንዘብ 15.600.00 (አስራ አምስት ሺ ስድስት መቶ ብር) መያዙን አስታውቀዋል፡፡
ኮሎኔል ፍቃዱ ለዚህ ኦፕሬሽን መሳካት ትብብር ያደረጉትን የአካባቢውን ማህበረሰብ አመስግነው የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የተለመደውን ትብብር ህዝቡ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ ዘገባው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።