በሶማሊያ ሴክተር 3 የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የ18 ወራት ተልዕኳቸውን አጠናቀው ተመለሱ፡፡

በሶማሊያ ሴክተር ሦስት 5ኛ ዙር ብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት የተሰጣቸውን ሃገራዊና አህጉራዊ ተልዕኮ በማጠናቀቃቸው ሴክተሩ የሽኝት ስነ-ሥርዓት አድርጎላቸዋል፡፡

በዚህ የሽኝት ስነ-ሥርዓት ላይ የሴክተር 3 ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጀኔራል ተክሉ ሁሪሳ የምስጋና ሰርተ-ፊኬት ከሰጡ በኋላ 5ኛ ዙር ብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን አባላት ሀገራችንና መንግስታችን የሰጣችሁን ተልዕኮ በስኬት በማጠናቀቃችሁ ልትደሠቱ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የሴክተሩ ሁለንተናዊ ወትሮ ዝግጁነትን በማጠናከርና ራሳችንን ከጥቃት ለመከላከል የሚያስችል ዝግጁነት ላይ እንድንገኝ ማስቻላችሁ፣  ከሴክተሩ ሞያተኞች ጋር በጋራ በመሆን በተለያየ ምክንያት ከስራ ውጪ የነበሩትን ብረት ለበስ፣ተሸከርካሪዎችን፣ከነፍስ ወከፍ እስከ የውጊያ ድጋፍ መሳሪያዎችን እና ሌሎች ንብረቶች  ጠግናችሁ ለሥራ ዝግጁ ማድረጋችሁ፣ ሐገራችን ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ገቢ እንድታገኝ አሥችሏችኋል ብለዋል።

ብርጋዲየር ጄኔራል ተክሉ ሁሪሳ ብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን ኢትዮጵያ በሠላም ማሥከበር ተልዕኮ ያላትን ከፍተኛ ተቀባይነት በማሥቀጠሉ ረገድ የበኩላችሁን ተወጥታችኋልና እናመሠግናለን ብለዋቸዋል።

ከሃገራችን ተቀብለን የመጣነውን ተልዕኮ በጥሩ ወታደራዊ ሥነ-ምግባር እና ያለደከመኝ ሰለቸኝ ተቀብለን የሚጠበቅብንን ሁሉ መፈፀም በመቻላችን ደስተኞች ነን ያሉት ደግሞ የብሄራዊ ድጋፍ ሰጪ ቡድን ሃላፊ  ኮሎኔል ገረመው ገመዳ ናቸው። በነበረን የ18 ወር የተልዕኮ ጊዜ ከሴክተሩ ሞያተኞች ጋር በመሆን በርካታ ሥራዎችን በመስራት የሰራዊታችንን ወትሮ ዝግጁነት ማጠናከር ችለናል ሲሉም ገልፀዋል፡፡

ዘጋቢ ሰመረ እሸቱ
ፎቶግራፍ አይናለም ተክለፃዲቅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።