ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 26 ቀን 2017 ዓ.ም
በአማራ ክልል የተገኘው ሠላም የሠራዊታችን ክቡር መስዋዕትነት ውጤት ነው ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ።
ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በሰሜን ጎንደር ዞን ከደባርቅ ወረዳ አስተዳደር የፀጥታ አካላት ጋር በዞኑ አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታ ላይ ውይይት ባደረጉበት ወቅት ሠራዊታችን በማይበገረው የዓላማ ፅናቱ እንዲሁም ጀግንነቱ ክልሉን ከፅንፈኛው መፈንጪያነት ወደ አስተማማኝ ሠላምና ልማት እንዲመለስ አድርጓል ብለዋል።
ፅንፈኛው ኃይል ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስና ስልጣንን ኢ-ህገ መንግስታዊ በሆነ መንገድ ለመያዝ በታሪካዊ ጠላቶቻችን እየተነዳ ያደረገው የቀቢፀ ተስፋ ሙከራ ከባድ ዋጋ አስከፍሎታልም ብለዋል ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ።
እኛ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስና ስልጣን በአቋራጭ ለመያዝ የሚመጡ ኃይሎችን ስርዓት እናስይዛለን እያደርግን ያለንውም ይሄንኑ ነው ያሉት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ዋጋ የከፈልንበትን ሠላም ማፅናትና በቁርጠኝነት መስራት ከአስተዳደር እንዲሁም ከፀጥታ አካለቱ የሚጠበቅ ቁልፍ ተግባር ስለመሆኑም አሳስበዋል።
በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠልና የአካባቢውን ሠላም መጠበቅ እንዲሁም ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ ከሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባም አቅጣጫ አመላክተዋል።
የዞኑ የፀጥታ ኃላፊዎችም ሚሊሺያ፣ ሠላም አስከባሪውና መደበኛ ፖሊስ ራሱን አደራጅቶ የክልሉን ብሎም የዞኑን ሠላም ለመጠበቅና ለማፅናት በትኩረት እየተሰራ ስመሆኑንም ተናግረዋል።
የአካባቢው ማህበረሰብ የፅንፈኛውን አድራጎት ተረድቷልም ተገንዝቧልም ያሉት የውይይቱ ተሳታፊዎች አሁንም ሠላሙን ለማፅናት ራሱን አደራጅቶ ስለ ሠላም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው ብለዋል። ዘጋቢ አንዷለም ከፍያለው ነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ