የሠራዊታችን የአሸናፊነት ብቃት እና መንፈስ በየደረጃው በሚገኝ አመራር ብቃት ይወሰናል።     ሌተናል ጀኔራል ደሳለኝ ተሾመ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ኢንስፔክተር ጀኔራል ቢሮ ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል ደሳለኝ ተሾመ በደቡብ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ተገኝተው ለሻለቃና ሻምበል አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል፡፡
    
ሌተናል ጀኔራል ደሳለኝ ተሾመ የተኪ አመራሮች ክህሎት በማሳደግ የሠራዊቱን የተኩስ አቅሙን በሥልጠና በማረጋገጥ ስልታዊ አቅሙን ማሣደግ፣ በእያንዳንዱ ግዳጅ ውጊያን መምራትና ማቀናጀት የሚችል ቀልጣፋ ውጤታማ በማድረግ በአጭር ጊዜና በአነስተኛ ኪሳራ ድልን የሚጎናፀፉ የነቃና የበቃ ሃይል በመገንባት ለሠራዊቱ አሸናፊነት አመራሩ የድል አስኳል ነው ብለዋል።
 
በሥልጠና ያገኛችሁትን እውቀት ተጠቅማችሁ ሃይል በመቆጠብ የዘላቂ ደህንነትን ለማስጠበቅና የብሄራዊ ጥቅምን ለማስከበር ብሎም የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ መሥራት የይጠበቅባችኋል ብለዋል።

የአካልና የአእምሮ ብስለትን በፅናት በመሰነቅ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ መሰናክሎች ውስጥ በጀግንነት የሚያልፍ ውሳኔ በፍጥነትና በብቃት የመወሰን ችሎታ ያለው የጋራ ዓላማን ለማሳካት በመደበኛ በኢ-መደበኛ ጦርነት ውስጥ የመስራት አቅሙን በማዘመን በተፈለገው ልክ ግዳጁን በስኬት መወጣት የሚችል ሃይል መገንባቱንም ሌተናል ጄኔራል ደሳለኝ ተሾመ አንስተዋል፡፡
 
የሃገርን ሉአላዊነት ለመጠበቅ ፅኑ ሃገራዊ አቋም ያለው ወታደራዊ አመራርና አባላትን መገንባታችንን አጠናክረን በመቀጠል የለውጥ ተግባራትን ውጤት በማስጠበቅ ህገ-መንግስቱንና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን መጠበቅ እንደሚገባ አመላክተዋል።

ሃገሩን ከማንኛውም ጥቃት መመከት የሚችል የተደራጀ ሃይል በመገንባት የኢትዮጵያን ሠላምና ልማት ለማሣካት ምንጊዜም መሥራት ዝግጁ መሆን እንደሚጠበቅ ገልፀው ሠራዊታችን በአንድነት በሃገራዊ ስሜት በጋራ የተሰጠውን ተልዕኮ በቁርጠኝነት መፈፀም እንደሚገባውም አመላክተዋል።

ዘጋቢ በላይ ታደለ
ፎቶግራፍ ቦጋለ አጊሴ

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።