የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በውጤት እየፈፀመ መሆኑ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራለ ሹማ አብደታ በከፍሉ አጠቃላይ የግዳጅ አፈፃፀም ብቃትና ውጤት ላይ በመወያየት የነበሩትን ድክመቶች በማስወገድ ጥንካሬዎችን አጎልብቶ ለላቀ የስራ አፈፃፀም መዘጋጀትን አላማ ያደረገ ውይይት ከዕዙ አመራሮች ጋር አካሂደዋል፡፡

በውይይቱ ወቅትም ዕዙ በበጀት አመቱ ባስቀመጠው ዕቅድ መሰረት ስኬታማና አመርቂ ስራዎችን መስራቱን የገለፁት አዛዡ በተለይ የተላላኪ ባንዳዎች ኢትዮጵን የማተራመስ ስትራቴጂን በመከታተል ከማኮላሽት አኳያ የላቀ ስራ መስራቱን ገልፀዋል፡፡

ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የቁርጥ ቀን ደራሽ በመሆኑ ሀገሩን ያሻገረ ዕዝ መሆኑን ገልፀው በመሆኑም የታሪካዊ ጠላቶቻችን ተላላኪ ባንዳዎች እጅ በመቁረጥ የህዝቦችን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ የመወሰን መብት እንዲከበር እዙ የሚጠበቅበትን ግዳጅ ውጤታማ በሆነ መንገድ ተወጥቷል ብለዋል፡፡

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ዕዙ ባደረጋቸው ስምሪቶችም በርካታ የፅንፈኛ አባላት እጅ እንዲሰጡ ተፅዕኖ በመፍጠር በርካቶች እጅ መስጠታቸውን አስታውሰው ክፍሉ በአዲሱ በጀት አመትም የዕዙን የግዳጅ አፈፃፀም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና የሚሰጡትን ሀገራዊ ተልዕኮዎች በጥራት በመፈፀም ዘላቂ ሀገራዊ ሰላምን በማረጋገጡ ሂደት ውስጥ የሚጠበቅበትን ሚና እንደሚጫወት አረጋግጠዋል፡፡

ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ጦርነትን ለማስቀራት ለጦርነት መዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን በማብራራት ዕዙ ከዚህ አኳያ ከአመራር ጀምሮ እስከ ተራ ተዋጊ በርካታ የአቅም ግንባታዎችን ባሳለፍነው ባጀት አመት ውስጥ በመስራት የማድረግ አቅሙን ከፍተኛ ማድረግ ችሏል ብለዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት ከሠራዊቱ ፊት ቆሞ የሚዋጋ ሀይል እንደሌለና የዘራፊነት እንጂ የተላላኪዎች የአሸናፊነት መንፈስ መኮላሸቱን ያብራሩት አዛዡ በቀጣይነት መንደር ለመንደር የሚቀማውን የፅንፈኛ ሀይል የመመንጠሩ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል።

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።