የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅ የአየር መከላከል ተገንብቷል።     ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር መከላከል በግዳጅ አፈፃፀማቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ክፍሎች እና አባላት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሂዷል።

በስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያን አየር ክልል በንቃት የሚጠብቅና ከማንኛውም ጥቃት የሚከላከል አስተማማኝ አየር መከላከል መገንባቱን አስታውቀዋል።

ታላቁ የህዳሴ ግድባችን በስኬት እንዲጠናቀቅ የምክትሉ አባላት የአየር ክልላችንን በጀግንነት በመጠበቅ ሃገርና ህዝብን ያኮራ ገድል ፈፅማችኋል በዚህም ልትኮሩ ይገባል ብለዋል።

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር መከላከል
ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ ባጫ በበኩላቸው ምክትሉ የሙያተኛውን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ እና የአየር መከላከል ትጥቆችንም ዘመኑን የዋጁ በማድረግ በኩል ሰፊ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረው በቀጣይነትም የሚሰጠንን ማንኛውንም ግዳጅ ለመወጣት በከፍተኛ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንገኛለን ነው ያሉት።

በመርሃ ግብሩ ለምክትሉ የግዳጅ አፈፃፀም ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱና ግዳጃቸውን በብቃት ለተወጡ ክፍሎች አባላትና አጋር አካላት የእውቅና እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።

ዘጋቢ ይታያል ምህረት
ፎቶግራፍ ባጫ ለገሰ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።