ዕዙ ማንኛውንም ተልዕኮ መፈፀም በሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል።     ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ

ዕዙ ከየትኛውም አቅጣጫ ሊሰነዘር የሚችል ጥቃትን መመከት በሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ ።

ዋና አዛዡ ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዕዙ የግዳጅ  ቀጣናዎች አሁናዊ የተልዕኮ አፈፃፀም ዙሪያ የመስክ ምልከታና  ቅኝት አድርገዋል።

ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ከከፍተኛ አመራሮቹ ጋር በነበራቸው ቆይታ የሠራዊቱ ዝግጁነትና ተልዕኮ አፈፃፀም የባዳውን ዕኩይ ሴራዎች መከታተልና መቆጣጠር በሚያስችል ደረጃ የተጠናከረ መሆኑን አንሰተዋል።

የባንዳዎቹ ተስፋ ከባዳዎቹ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ባንዳዎቹ ህይወታቸውን ለማቆየት ከባዳዎቹ የሚጠብቁት ፍርፋሪና ባዳዎቹ በህገወጥ መንገድ ማግበስበስ የሚፈልጉት የኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት በጠንከራ ቁጥጥርና ክትትል የበለጠ መጥበብ አለበት ሲሉም አሳስበዋል።

የሠራዊቱ አሰፋፈር፣ ቁርጠኝነትና የስነ-ልቦና ዝግጁነት ከመቼውም ጊዜ የላቀ ነው ያሉት ዋና አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ባዳዎቹ ስለ ኢትዮጵያ ምንም ሊያስቡ ይችላሉ ነገር ግን ለመተንኮስ ሲያስቡ ከባድ ዋጋ እንደሚከፍሉም ጭምር ማሰብ ይገባቸዋልም ብለዋል።

በፅንፈኛው ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጃ በላኪውም ሆነ በተላላኪው ላይ ድንጋጤ ፈጥሯል ያሉት አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ የሠላም አማራጭ በማይከተሉ፣የኢትዮጵያን ልማት በሚያደናቅፉና የባዳዎቹን ተልዕኮ ለማስፈፀም በሚፍጨረጨሩ ኃይሎች ላይ የምንወስደው እርምጃ ጠንከር ያለ ነው ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ዘገባው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።