ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል፦   ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ኀዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያና አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋትን ለማረጋገጥ በሚያስችላቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዘዥ ጄኔራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰን የተመራ ልዑክ ከኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱ በአፍሪካ ቀንድ ሠላምና መረጋጋትን ለመፍጠር የቀጠናው ሐገራት በትብብር መሥራት እንዳለባቸውም ነው የተመላከተው።

ሁለት ሐገራት ወታደራዊን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ለበርካታ ዓመታት በትብብር እየሠሩ መምጣታቸውን ያነሱት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተች ትገኛለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎቷ ለሠላማዊና ኢኮኖሚዋን ለመገንባት መሆኑን ያብራሩት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ከአሜሪካ ጋር ያለው ወታደራዊ ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንደገለፁት ኢትዮጵያ አልሸባብን ለማዳከምና የሽብር ሴራውን ለማክሸፍ የምትወስደውን የኃይል እርምጃ  አጠናክራ ትቀጥላለች።

ኢትዮጵያ በቀጠናው ፀጥታን ለማስፈን እየተጫወተች ያለችውን ሚና ያደነቁት የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄነራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰን ሽብርተኝነትን በጋራ የመዋጋት ሥራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሠላማዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገውን መንገድ እንደሚደግፉ የገለፁት  የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዛዡ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ ብትወጣ የበለጠ ለቀጠናው ሠላም ትሠራለች ብለው እንደሚያምኑ ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ በኩል ያሉ ፍላጎቶችንና በቀጠናው ሠላምን ለማረጋገጥ ስለያዘቻቸው ዕቅዶች ከዋሽንግተን ዲሲ ባለሥልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩም ጠቁመዋል።
በዕለቱ “የአፍሪካ ቀንድ የሠላም ሁኔታ” በሚል ርዕስ በኮሎኔል መስፍን አውላቸው ጥናታዊ ፅሑፍ ቀርቦ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ሁለቱ ሐገራት ስጦታ ተሰጣጥተዋል።

ዘጋቢ ውብሸት አንበሴ
ፎቶግራፍ አበረ አየነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።