ህገ-ወጥ የመሳሪያ አዘዋዋሪዎች ላይ የሚደረገው ከትትል ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ልዩ ስሙ አስጎሪ በተባለ ቦታ ህገ-ወጥ መሳሪያ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

በስፍራው የተሰማራው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል ክፍለጦር ባደረገው የተቀናጀ ክትትል ህገ ወጥ መሳሪያው በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፍቃዱ ጥላሁን ገልፀዋል፡፡

ክፍሉ በአካባቢው ከተሰማራበት ጊዜ ጀምሮ በቀጠናው ሰላም ለማስፈን የሽብር ቡድኖችን እየተከታተለ በመደምሰስ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሰላም ማስፈኑን ገልፀው የሽብር ቡድኑ ለጥፋት ተልዕኮ የሚጠቀምበትን የህገ-ወጥ መሳሪያ ዝውውር እና ንግድ ከምንጩ ለማድረቅ በአቅራቢዎችና በተቀባይ የጠላት ህዋሶች ላይ የሚደርገው ቁጥጥር የተሳካ ውጤት እያመጣ ይገኛል ብለዋል፡፡

ሰሞኑን በተደረገው ክትትል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችና ሽጉጥ፣ የብሬንና ልዩ ልዩ ተተኳሾች መያዛቸውንና ህገ-ወጥ መሳሪያ የሚገበያዩበትን ገንዘብ 15.600.00 (አስራ አምስት ሺ ስድስት መቶ ብር) መያዙን አስታውቀዋል፡፡

ኮሎኔል ፍቃዱ ለዚህ ኦፕሬሽን መሳካት ትብብር ያደረጉትን የአካባቢውን ማህበረሰብ አመስግነው የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የተለመደውን ትብብር ህዝቡ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ ዘገባው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ