መብረቅ ክፍለጦር በወሰደው ርምጃ የሽብር ቡድኑ ዋና ዋና አመራሮቹ ተመቱ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

መብረቅ ክፍለ ጦር ሰሞኑን ባደረገው ዘመቻ የአሸባሪው ሸኔ አመራሮችና አባላት ሲመቱ መገናኛ ሬዲዮን ጨምሮ በርካታ የጦር መሳሪያ እና ተተኳሽች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ ቄለም ፣ ግራይ ሶንካና አቦቴ አካባቢ የሸኔ ሽብር ቡድን ላይ በተሰነዘረ ማጥቃት ጃል አብዲ፣ ጃል ጉርሜሳ፣ ጃል በዳሳ ተስፋዬና ጃል ገመቹ የተባሉ አራት ዋና ዋና አመራሮቹ ተገድለዋል።

የመብረቅ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ንጉሴ ጥላሁን እንዳሉት፦

ከአመራሮቹ መደምሰስ ባለፈ በርካታ አባላቱ ሙት ሆነው በአካባቢው ይንቀሳቀስ የነበረው የሽብር ቡድኑ የመገናኛ ሬድዮ፣መሳሪያና ተተኳሽ በመማረክ አቅሙን ማንኮታኮት ተችሏል።

ምክትል አዛዡ ጨምረው እንዳስረዱት ከመሳሪያና ተተኳሾች ባለፈ የተለያዩ ቁሳቁሶች የተማረኩበት ሲሆን በዚህኛው ዘመቻ በርካታ ሃይል ለማሰለፍ የሞከረው ሸኔ ከፍተኛ ምት ደርሶበታል።

ለሽብር ቡድኑ መደምሰስ የአካባቢው ማህበረሰብ ከክፍለ ጦሩ ጋር በቅንጅት መስራቱ ከፍተኛ ሚና እንደነበረው የክፍለጦሩ አመራሮች በአስተያየታቸው የገለጹት።

ዘጋቢ ዮሴፍ ጉርቢያው

ፎቶግራፍ ዮሴፍ ጉርቢያው

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ