ለምንም አይነት ፈታኝ ሁኔታዎች የማይበገር ጠንካራ ሠራዊት ተገንብቷል።   ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

ግዳጁን በፅናት የሚፈፅምና በምንም አይነት ፈታኝ ሁኔታዎች የማይበገር ጠንካራ ሠራዊት ተገንብቷል ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ።

ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በሠራዊቱ የግዳጅ ቀጠና ተገኝተው ሠራዊቱን ባበረታቱበት ወቅት የኢትዮጵያን ሠላምና ዕድገት የማይሹ ቅጥረኞች በሠራዊታችን ጠንካራ ክንድ የእጃቸውን አግኝተዋል ሲሉ ተናግረዋል።

ለኢትዮጵያ ሠላም የምንከፍለው ዋጋ ያኮራናል ያሉት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በተሳሳተ ስሌት የገመገሙን ታሪካዊ ጠላቶቻችንና ተላላኪ ባንዳዎቻቸው የሃፍረት ካባቸውን ተከናንበዋልም ብለዋል።

በኢትዮጵያና ህዝቦቿ ክብር መቼም ቢሆን እንደማንደራደር ታሪካዊ ጠላቶቻችን ጠንቅቀው ያውቁታል ያሉት አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ለዚህም ትንኮሳ አድርገው ሠላሟን ለማደፍረስ የተፈታተኗት ሁሉ የደረሰባቸውን ውርደት ያስታውሱታልም ብለዋል።

እኛ ሁሌም አሸናፊ የምንሆነው የቆምንለትን አላማ  ጠንቅቀን ስለምናውቅና የኢትዮጵያ ወታደሮች ስለሆንን ነው ያሉት አዛዡ  ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ፅናት፣ቁርጠኝነትና አይበገሬነታችሁ የዚሁ ማረጋገጫም ነው ብለዋል።

በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆነን መጪውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ ወታደራዊ ዝግጁነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን፤ ህገመንግስታዊ ተልዕኳችንንም በፅናት እንፈፅማለን ሲሉም ተናግረዋል።

የሠራዊቱ አባላት በበኩላቸው የቀጣናውን ሠላም አሰተማማኝ ለማድረግ በርካታ ስኬታማ ተልዕኮዎችን ስንፈፅም ቆይተናል አሁንም ማንኛውንም ግዳጅና ተልዕኮ በጀግንነት ለመፈፀም እንደ ግልም ይሁን እንደ አሃድ ዝግጁነታችን ከመቼውም ጊዜ የላቀ ነው ብለዋል።

ዘገባው የአንዷለም ከፍያለው ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

http://localhost/defensenew

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ