ስፖርትና ሠራዊት የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ገፅታዎች።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

ዛሬ ላይ የአለምን ህዝብ ወደ አንድ አካባቢ ያሰባሰበ መሠረታዊ ጉዳይ ነው ስፖርት። ስፖርት በሠራዊታችን ዘንድም የተለዬ ቦታ አለው። ከተፈለገው ግብ ለመድረስ፣ በአካል ብቃት ዳብሮ ለመገኘት፣ ግዳጅን በውጤት ለመፈፀም፣ ብቻ ሠራዊቱ ተልዕኮውን ቀለል አድርጎ በድል መፈፀም እንዲችል ስፖርት ዓይነተኛ ሚና አለው።

የእርስ በእርስ ዝምድናን ለማጠናከር፣ አሃዷዊ ፍቅርን ለማሣደግ፣ ግዳጅን በጋራ ለመወጣት፣ አብሮነትን ለማሥፋት ብቻ ስፖርት ለብዙ ነገሮች የሚረዳ በመሆኑ በሠራዊቱ ዘንድ በተለዬ መንገድ ትኩረት ተሠጥቶት የውድድር መድረኮች ይዘጋጃሉ በከፍተኛ ሞራል ውድድሮች ይካሄዳሉ።

ብቻም ሳይሆን እንደተቋም መከላከያን ወክለው ሊወዳደሩ የሚችሉ ብቃት ያላቸውን ስፖርተኞች ለመመልመልም ውድድሩ የራሱ የሆነ በጎ ገፅታ አለው።

ከውድድር በዘለለ በሠራዊቱ ዘንድ የሚካሄደው የዕለተ እረቡ የማሥ ስፖርትም ዘርፈ ብዙ አሥፈላጊነት ያለው በወዳጅነት ላይ የተመሠረቱ ውድድሮችን ለመፍጠር የሚያግዝ ነው።

የሠራዊቱ አባላትም ይህን ታሣቢ ያደረገ ከቁምነገሩ ጎን ለጎን እያዝናና አንድነትን የሚያጠናክር የእርስ በእርስ ውድድሮችን በእግር ኳስ ፣በመረብ ኳስ፣ በአትሌቲክስ፣ በገመድ ጉተታና በሌሎች የስፖርት ዓይነቶች ማካሄድ የዘወትር ተግባራቸው ነው።

በውብሸት ቸኮል

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ