በትጥቅ የመከላከያ ሠራዊቱን የዝግጁነት ደረጃ ለማሣደግ እየሠራን ነው  አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም

በትጥቅም ሆነ በትጥቅ ግብዓቶች የመከላከያ ሠራዊቱን የዝግጁነት ደረጃ ለማሣደግ በውጤት እየሠራን ነው ሲሉ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም ተናገሩ

ቆየት በሚል ስያሜው የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በሚል ሲጠራ የነበረው አሁን ላይ ተቋሙ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በደንብ ቁጥር 567/2017 በመፅደቁ የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ በመባል አድማሱን በማስፋት በርካታ ኢንዱስትሪዎችን አካቷል።

ለመከላከያ ሠራዊት የተለያዩ ትጥቆችን እና የትጥቅ ግብዓት ምርቶችን በማምረት እና የተለያዩ የኮሜርሻል ምርቶችን በማምረት እንደ ተቋም ብሎም እንደ ሀገር ብቸኛው ተቋም ከመሆኑ አንፃር ትልቅ የሃይል አቅም በመሆን ዘርፈ ብዙ በቴክኖሎጂ የታገዙ ተግባራትን እያከናዎነ እንደሚገኝ የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም ገልፀዋል።

መንግስትና ተቋሙ ለመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠታቸው በሪፎርሙ አዳዲስ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም የምርትና ምርታማነትን በማምረት የሠራዊቱን የዝግጁነት አቅም በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሃብት አስተዳደር ዘርፍ ኮሎኔል ዩሃንስ ትኬሳ በበኩላቸው እየተመዘገበ ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለተቋሙ ብሎም ለሀገራችን ከፍታ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

የመከላከያን ፍላጎት ለማሟላት የኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፑ አመራርና ሠራተኛ በአንድ እስትንፋስ ምርትና ምርታማነትን በማሣደጉ ረገድ ሥራቸውን በአግባቡ በመፈፀም ሀገራዊ ተልዕኳቸውን በስኬት የመወጣቱን ሂደት አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ኮሎኔል ዩሃንስ ተናግረዋል።

በመስከረም ብርሃኔ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ