ተቋሙን የሚመጥን ሎጀስቲክሳዊ ስራ ከምንጊዜውም በላይ እየተሠራ ነው፡፡ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምን ለአራት ቀናት ተመልክቷል።

የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ  ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል የዘንድሮው የእቅድ አፈፃፀም ውይይት ከወትሮው ለየት የሚያደርገው ሀገራችን ባከናወነቻቸው ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ተግባራት በዓለምአቀፍ እና አህጉራዊ መድረኮች ያላት ተቀባይነት እና ተደማጭነቷ እያደገ በመምጣቷ በተቋማችንም በወታደራዊ ዘርፉ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የሚደረጉ የወታደራዊ ጉዳዮች ትብብር እያደገ ሀገራት ከእኛ ጋር በትብብር ለመስራት የተነሱበት ወቅት መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

በዋና መምሪያው ስር የሚገኙ የመምሪያ እና የክፍል ሃላፊዎች በተሰጣቸው ተልዕኮ እና በእቅዱ መሰረት አፈፃፀማቸውን በማስመልከት ባቀረቧቸው ሪፖርቶች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደተቀመጠው በበጀት ዓመቱ ዋና መምሪያው የሠራዊቱን ሁለንተናዊ ዝግጁነት በማረጋገጥ ረገድ በሁሉም ዘርፍ የተሻለ ውጤት የተመዘገበበት ሰፊ ስራ ተሠርቷል።
 
የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል በመርሐ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ አፈፃፀማችን የተቋማችንን ፈጣን ለዉጥ ታሳቢ በማድረግ፣ ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጡ ትጥቆች በውስጥ አቅም በማዘጋጀት ወጪን በመቀነስ፣ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን እና ወጤታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ዝግጁነታችንን ያረጋገጥንበት የአፈፃፀም ብቃት ከፍ ብሎ የታየበትና አዳዲስ የስራ ባህል የተላመድንበት አመት ነው ብለዋል።

የሰራዊቱን የዕለት ተዕለት ቀለብ፤ አልባሳት፣ ትጥቅ እንዲሁም ሞብሊቲን በማረጋገጥ የውጊያ ድጋፍ አገልግሎት አሰጣጡን እያሳለጠ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በልማቱ ዘርፍም በተቋማችን እንዲተገበሩ የታቀዱ የልማት ስራዎች ውስጥ የማዕከሎች የግንባታ ስራ በማጠናቀቅ እና በማልማት አመራሩና ሙያተኛው የተሰጡትን ተልዕኮዎች በአግባቡ አሳክቶ ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያደርስ፤ የሥራ ተነሳሽነቱ ይበልጥ እንዲጨምር መደረጉንም አንስተዋል።

በአዳዲስ ሀሳቦች ችግር ፈቺ ወጪ ቆጣቢ አሰራሮች ላይ አተኩሮ እንዲሰራ ማዕከላቱን ውብ፣ ፅዱ እና ለስራ የተመቹ የማድረግ ስራ መሠራቱን ገልፀዋል።

ሌተናል ጄኔራል አብዱራህማን ኢስማኤል በተቋማችን የተጀመረውን የሪፎርም ትግበራ የሚያሳኩ፣ የአመራሩንና የሙያተኛውን የመፈፀም አቅም የሚያሳድጉ የሰነ-ልቦና ግንባታዎች፣ ስልጠናዎች በተከታታይ በመከናወናቸው አሁን ላይ በሙያዊ ስነ-ምግባር የታነፀ ወታደራዊ ባህል እና ጨዋነትን ያከበረ የተቋቋመበትን ተልእኮ እና የሚሰጠውን ግዳጅ ታሳቢ ያደረገ አባላት መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።

በሰላምም ሆነ በውጊያ የሚኖር ተልዕኮን በማገናዘብ፣ ሃብትን በአግባቡ የሚያስተዳድር፣ ቀልጣፋ፣ የማይቋረጥ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ የውጊያ አገልግሎት ድጋፍ በተፈለገው ጊዜና ቦታ በፍጥነትና በጥራት መስራት የሚያስችል የሎጀስቲክስ አቅም የተፈጠረ መሆኑ በውይይቱ ተገልፃል፡፡ ዘገባው የወርቅነህ ተስፋው ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
http://localhost/defensenew/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.co

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ