የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሃመድ እና በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ በመከላከያ ሠላም ማስከበር ማዕከል የአለም አቀፍ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አሁናዊ የስራ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።
ጉብኝቱ በፈረንሳይ መንግስት የሚሰጡ አጫጭር ስልጠናዎች በሠላም ማስከበር ተሳትፎ ላይ ያላቸውን አዎንታዊ ገፅታ ለመመልከት እና ቀጣይ በሚሰጡ ስልጠናዎች በጋራ ለመስራትና ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ ጉብኝቱ የሁለቱን ሀገራት ሕዝብና መንግስት የረጅም ጊዜ ወዳጅነት ለማጠናከር እንደሚረዳ ገልፀው ቀጣይ በሚሰጡ ስልጠናዎች ከማሰልጠኛ ኢንስቲትዩቱ ጋር በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሃመድ በበኩላቸው የፈረንሳይ መንግስት የሚሠጠው አጫጭር ስልጠና አለም አቀፍ የሠላም ማስከበር ግዳጃችንን በተሻለ መንገድ እንድንፈፅም እገዛ የሚያደርግ ነውና ለቀጣይም የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡
የመከላከያ ሠላም ማስከበር ማዕከል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አዳምነሀ መንግስቴ የፈረንሳይ መንግስት እያደረገ ሥላለው ድጋፍ በመከላከያ ሠላም ማስከበር ማዕከል ስም አመሥግነዋል፡፡
ዘጋቢ ተፈራ ጥላዬ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
http://localhost/defensenew/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av





