የሀገራችንን ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሰራዊቱንና የአመራሩን ብቃት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።

ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ በአጭር ኮርስ ያሰለጠናቸውን የክፍለ ጦር አመራሮችን አስመረቋል።

በምረቃው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ሀላፊ ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን ባስተላለፉት መልዕክት ወቅታዊ ፣ ውስጣዊ ፣ ቀጠናዊና አካባቢያዊ ሁኔታዎችን የተረዱ ብቻ በሳይንሳዊ መልኩ የሚተነብዩ አመራሮችን ለማፍራት የኮሌጁ ሚና የላቀ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አመራሮቹ በተግባራዊ ውጊያ የተፈተኑና የውጊያ ልምድ ያላቸው መሆኑን የጠቀሱት ሀላፊው ስልጠናው  ተለዋዋጭ ወታደራዊ ሁኔታዎች እንዲገነዘቡ ያደረገ ተግባር ተኮር ስልጠና መሰጠቱ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።

መከላከያ የሀገራችንን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ዘመናዊ፣ ፕሮፌሽናልና ዲሲፒሊንድ የሆነ ሰራዊት ለመገንባት እያደረገ ያለው ጥረት ውጤታማ መሆኑን ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዘመናችን ውጊያዎች ውስብስብ ፣ ዘመናዊና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም የሚጠይቁ መሆናቸውን የገለፁት ሀላፊው፣ ለዚህም ያልተቋረጠ ስልጠና ወሳኝ መሆኑንና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም  ገልፀዋል።

ተመራቂ ከፍተኛ መኮንኖቹ ያላቸውን የረጅም ጊዜ የውትድርናና የአመራር ልምድ ካገኙት ስልጠና ጋር በማዋሀድ አሀዶቻቸውን ማደራጀት ማብቃትና በተፈለገው ጊዜና ቦታ የሚሰጣቸውን ግዳጅ በመፈፀም ሀገራቸውን ማኩራት እንደሚኖርባቸውም አሳስበዋል።

በዝግጅቱ ላይ የመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ምክትል ሀላፊ ለአመራር ስልጠና  ሜጀር ጀነራል ሰለሞን  ቦጋለን ጨምሮ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮችና የኮሌጁ ማህበረሰብ ተገኝተዋል።

በብዙአየሁ ተሾመ

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ