የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን የአንደኛ ዲቪዚዮን የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት አዘጋጅነት ከጥር 04 ቀን እስከ ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው የአንደኛ ዲቪዚዮን በመቻል ሁለተኛ ዲቪዚዮን በአቃቂ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ  አሸናፊነት ተጠናቋል።

በመዝጊያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ለአሸናፊ ቡድኖች የዋንጫ እና ሜዳሊያ የሠጡት የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፕሬዘዳንት የእሳት እና ድንገተኛ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አህመድ መሃመድ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ናቸው።

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታ መቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን የሚኒሊክ ሆስፒታል አቻውን 3ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል። መቻል ባለድል የሆነበትን ሶስቱንም ጎሎች አስር አለቃ አንተነህ ጌታቸው ከመረብ አሳርፏል።

የውድድሩ ኮከብ አሰልጣኝ የመቻሉ ሻምበል ወንደወሰን በየነ ሲሆን ፣ 10 ጎሎችን በማስቆጠር መቶ አለቃ ደረጄ ግዛው ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ፣ አምሳ አለቃ ግርማ ገቢሳ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ሶስቱም ከመቻል አሸናፊ በመሆን ሽልማታቸውን ከክብር እንግዶች ተረክበዋል ።

የመቻል ጤና እግር ኳስ ቡድን በሃልም ኢንተርናሽናል እና በአንበሳ ስፖርት ትጥቅ አምራች ስፖንሰር አድራጊነት በተደረገው የእግር ኳስ ውድድር በይቻላል አንድ ለዜሮ ተሸንፈው ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ የብር ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኗል።

ወድድሩ የሚቀጥል ሲሆን በ18ኛው የመንግስት መስሪያ ቤቶች የእግር ኳስ ውድድር መከላከያ ሠራዊት እግር ኳስ ቡድን ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር ሰኞ ሰኔ 01 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም የፍፃሜ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በተያያዘ ዜና የመቻል ከ17 ዓመት በታች የሮሃ አቻውን 8ለ0 በሆን ሰፊ ውጤት አሸንፏል።

በገረመው ጨሬ

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ