የመከላከያ ሚኒስቴር ባለፉት ዘጠኝ ወራቶች አበረታችና ውጤታማ ተግባራት አከናውኗል- ኢንጂነር አይሻ መሀመድ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀም ውይይት አድርጓል። የሥራ አፈፃፀም ሪፖርቱን ያቀረቡት የሚኒስቴሩ እቅድ እና ሪፖርት ዝግጅት ክትትል ዳይሬክተር ኮሎኔል ፈይሳ ታደሰ በአንዳንድ ክፍሎች ላይ በስራ ሂደት እንቅስቃሴ ውስጥ ካጋጠሙ ችግሮች እና ከታዩ ክፍተቶች ውጭ ሁሉም ፈፃሚ አካላት ስራቸውን በትጋት በመፈፀማቸው አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል።

ሠራዊቱን ከአዳዲስ ቴክኖሎጅ ጋር በማዋሀድ በአስተማማኝ መልኩ ሠላምን እንዲጠብቅ በማድረግ በኩል ከፍተኛ ተግባራት መከናወኑን አንስተዋል። የኢንዱስትሪዎችን አቅም በማሳደግ፣ ወታደራዊ ዲፕሎማሲውን ከፍ በማድረግ፣ የሰው ሀብት አቅምን በማደራጀት እና በማዘመን፣ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ትምህርታዊ፣ ሙያዊ እና ወታደራዊ ስልጠናዎች የመስጠት ሥራዎች መተግበራቸውም ተመላክቷል።

የተቋሙን ገፅታ መገንባት፣ የሙስና ወንጀሎችን መከላከል፣  ለደንበኞች ፍትሀዊ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት፣ የስርዓተ- ፆታን ግንዛቤ ማሳደግ በአጠቃላይ ተቋሙ በተሰማራባቸው የስራ ዘርፎች  አበረታች ውጤት መገኘቱ በውይይቱ ተገልጿል።

ከተወያዮች የተነሱ ሀሳቦችን እና ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግ ማብራሪያ የሰጡት የመከላከያ ሚኒስትሯ  ኢንጂነር አይሻ መሀመድ ባለፉት ዘጠኝ ወራቶች የተሠራው አጠቃላይ ሥራ ውጤታማና የሚበረታታ መሆኑን ገልፀው በአራተኛው ሩብ ዓመት ይበልጥ የተሻለ የእቅድ አፈፃፀም ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም ራሱን ዝግጁ ማድረግ እና መታተር እንደሚገባው አመላክተዋል።

ፈፃሚ አካላት የተቋሙን ታላላቅ ግቦች መሰረት ያደረገ የእቅድ አፈፃፀም ውጤት ሊኖራቸው እንደሚገባ

አሳስበው መከላከያ ታላቅ አቅም ያለው አንጋፋ ተቋም በመሆኑ ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ ወደ ውጤት ለመቀየር ከዚህ በላይ ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በብርሃን እንዳየሁ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

as1
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን የመከላከያ ሚኒስትሯ ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ።
as
ኢትዮጵያ እና ኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቢል ) በወታደራዊ መስኮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
s6
በአምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ የተፃፈው ''የፀረ-ሽምቅ ውጊያ ጥበብ'' መፅሐፍ ተመረቀ።
mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።

ስፖርት

as1
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን የመከላከያ ሚኒስትሯ ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ።
as
ኢትዮጵያ እና ኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቢል ) በወታደራዊ መስኮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
s6
በአምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ የተፃፈው ''የፀረ-ሽምቅ ውጊያ ጥበብ'' መፅሐፍ ተመረቀ።
mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ