የኮር እና የክፍለጦር አመራሮች
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
የሚሰጠውን ማንኛውንም ውስብስብና ፈተኝ ግዳጆች በድል መወጣት የሚችል ሠራዊት ተገንብቷል ሲሉ የስድስተኛ ዕዝ ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጄነራል ሃብታሙ ምህረቴ ተናገሩ።
የዕዙ የሠራዊት አባላት በውስብስብ ሁኔታዎች ሳይበገር ህዝብና መንግስት የሰጡትን ተልዕኮዎች በጀግንነት፣ በውጤታማነትና በድል እየተወጣ የህብረተሰቡን ሰላም እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት አመራሮቹ በተደረጉ የስምሪት ስራዎች የላቀ ውጤት ማስመዝገቡንና አስደናቂ ገድሎች መፈፀማቸውን አውስተዋል።
ሠራዊቱ በተሰማራባቸው የግዳጅ ቀጠናዎች ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር በተደረጉ ሰፋፊና ተከታታይ ህዝባዊ መድረኮች አሸባሪው የሸኔ ቡድን እና ፅንፈኛው ፈጥረውት የነበረውን ችግር ማጥራት የተቻለ መሆኑን ተናግረዋል።
የዕዙ አባላት ሞራላዊና ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነት የመገንባት ፣ የአሃዱዎችን ግዳጅ የመፈፀም እና የማድረግ አቅሞች የማሳደግ ፣በየደረጃዉ የሚገኙ አመራሮችን ዙሪያ-መለስ የመምራት አቅም የማጎልበት እንዲሁም የተለያዩ ሙያተኞችን በየተመደቡበት ዘርፍ ሙያዊ ብቃታቸዉን የማሳደግ ስራ በስፋት መሠራቱን ገልፀዋል።
ስልጠናዎችም የዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ ሂደቱን መነሻ በማድረግ ከውጊያ ፅንሰ-ሃሳብ ጀምሮ እስከ አሃድ መምራትና ለዉጊያ ማዘጋጀት እንዲሁም ግዳጅ ተኮር የስልጠና ስምሪት በማከናዎን ተደማሪ የማድረግ አቅሞችን ለመፍጠር በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዘጋቢ አዲሱ አራጋው
ፎቶግራፍ ሌሊሴ አራራሜ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ





