የሚዲያ ስራችን በሠራዊታችን ተልዕኮና ግዝፈት ልክ መቃኘት ይኖርበታል።ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

ከመከላከያ ክፍሎች ለተውጣጡ የሥነ ልቦና ግንባታ አመራሮች እና የሚዲያ ሙያተኞች ሲሰጥ የቆየው ሰልጠና ተጠናቋል። በዚሁ የሰልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ሰራዊት ሰነ- ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ሰራዊታችን የተሠጠውን ሀገራዊና ህዝባዊ አደራ መሠረት አድርጎ የሚያከናውነው ህዝባዊና ሀገራዊ ተልዕኮ በሚገባ አልተነገረለትም ብለዋል።

ይህንን አካሄድ ለማስተካከል የሰራዊቱን ልፋትና ድካም የሚረዱ በእያንዳንዱ ግንባር ድል  ያደረጉ ብዕርና ወረቀታቸውም የጠላትን ሀሰታዊ ፕሮፖጋንዳ ከንቱ የሚያስቀር ጀግና ወታደራዊ ጋዜጠኞች ማፍራት ላይ

ትኩረት በማድረግ እየተሠራ ሥለመሆኑ አንስተዋል።

የሠራዊታችንን ሰነ ልቦና በውጊያም ሆነ ከውጊያ በኃላ ሳይቆራረጥ ተከታታይ በሆነ መልኩ መሰራት ያሥፈልጋል ያሉት ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ይህ የሚሆነውም የስነ ልቦና ግንባታ የሰራዊታችን የአሸናፊነት ሰንቅ ሰለሆነ ነው ብለዋል።

ሰራዊቱ የሚፈፅመው አኩሪ ተጋድሎ በሚዲያዎቻችን ለህዝባችን እንዲደርስ በተቋሙ ክፍሎች ያሉ የሚዲያ ሙያተኞች ጠንክረው መስራት አለባቸው ያሉት ጀነራል መኮንኑ ስልጠናው የተሰጠውም ከዚህ  አላማ አንፃር መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ አሁን ላይ የሚዲያ ነፃነትን በመጥፎ ጎኑ በመጠቀም የሰራዊታችንን ሰምና ዝና ለማጥፋት የሚጥሩ ሃይሎች ያሉ በመሆናቸው የእነዚህን እኩይ ሃይሎች የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ተከታትሎ ማጋለጥ ይገባልም ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሜጀር ጀኔራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት ያገኛችሁትን አቅም በመጠቀም የሰራዊታችንን የዕለት ተዕለት ተልዕኮና እሱን ተከትሎ የሚያስመዘግበውን አኩሪ ተጋድሎ ለሚዲያ ሽፋን በሚሆን መልኩ መሰነድ ፣ መዘገብ ይጠበቅባችኋል ሲሉም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚን ጨምሮ ለሥልጠናው መሳካት ከፍተኛ አሥተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ሜጄር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን ምስጋና አቅርበዋል።

አጠቃላይ የሥልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የዋና ዳይሬክቶሬቱ የሥልጠና ቡድን መሪ ኮሎኔል መንግስቱ ካታንጋ ስልጠናው በተመደበለት የአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በንድፈ ሃሳብና በተግባር ለሥነ ልቦና አመራሮችና ለሚዲያ ሙያተኞች በቀንና በማታ የተሠጠ መሆኑን ጠቁመው ስልጠናው በየክፍላቸው በተግባር ከሚያከናውኗቸው የግንባታ ስራዎች ጋር አያይዘው እንዲመለከቱት መደረጉንም ተናግረዋል፡፡

በማሩ ግርማይ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com

@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ