የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል የፀረ-ሰላም ሀይሎችን እንቅስቃሴ በመግታት መስዋዕትነት ከፍሎ ሀገርን ከመፍረስ የታደገ ክፍል ነው ሲሉ ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ተናገሩ።
ክፍሉ በውጊያ ውስጥ ሁኔታን የሚቀይር ለሌሎች ክፍሎች የውጊያ እንቅስቃሴን የሚያመቻች ጀግና እና አርአያ የሆነ ክፍል ነው ብለዋል።
የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል በአጭር ጊዜ በመደራጀት በርካታ የሀገር መሪዎችን እና ዲፕሎማቶችን ደህንነት በተሟላ መንገድ የመጠበቅ ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ መፈፀሙን ገልፀዋል።
ጀኔራል ጌታቸው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል አባላት ዘንድሮ የተመዘገበውን ውጤት ቀጣይም አስጠብቃችሁ በተሻለ ውጤት እንደምታስቀጥሉ እምነቴ የፀና ነው ብለዋል።
በአመቱ ከጓድ መሪ ጀምሮ እስከ ሻለቃ አመራር ድረስ የተሰጠው ስልጠና እንዲሁም በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የተሰጡ የተለያዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎች ክፍሉ የተሻለ የማድረግ አቅም እንዲኖረው ያሥቻለ መሆኑን ገልፀዋል።
የጥበቃ ሃይሉ የተለያዩ ሀገር ዲፕሎማቶችን በክብር በመቀበልና በመሸኘት የሀገርን ገፅታ በመገንባትና መሪዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ የተለያዩ አለማቀፋዊ እና አህጉራዊ ስብሰባዎች በስኬት እንዲጠናቀቁ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በአስተማማኝ ሁኔታ የቆመለትን አላማ እየፈፀመ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በመዝገቡ ያረጋል





