የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለሶማሊያ ህዝብ ውድ ህይወቱን ከፍሏል ህዝባዊነቱንም አሳይቷል።

የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

የደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ ከልል መንግስት የሴክተር 3 ዋና አዛዥ ሆነው ለቆዩት ብርጋዲየር ጀኔራል በስፋት ፈንቴ እና ለአዲሱ የሴክተር 3 ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጀኔራል ተክሉ ሁሬሳ የአሸኛኘትና የአቀባበል ሥነ-ስርዓት አካሂዷል፡፡

በዝግጅቱ ላይ የሃገር ሽማግሌዎችን በመወከል መላቅ መሃመድ ያቁብ ሼክ ዴሮው፣የክልሉን ሚኒስትሮች በመወከል  የደቡብ ምዕራብ ሱማሊያ ኢንቨስትመንት እና ዕቅድ ሚኒስትር አቶ አብድሃኪም መሀመድ ሃጂ ፊቅ፣የባይድዋ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱላሂ ወቲን፣የባይ ዞን አስተዳደር አቶ አሊ ወርዴር ዶዮው የክልሉን መንግስት ወክለው ዕውቅናና ሽልማት አበርክተዋል።

ተወካዮቹ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለሶማሊያ ህዝብ ለረጅም አመታት ውድ ህይወቱን የከፈለ አስካሁንም ድረስ ህዝባዊነቱ፣የግዳጅ አፈፃፀሙ በሶማሊያ ህዝብ የተመሰከረለትና በህዝብ ላይ ምንም ዓይነት ችግር እንዲደርስ የማይፈቅድ ቀጠናችንን ከመጠበቅና ሰላምን ከማረጋገጥ ባለፈ የተቸገሩትን በምግብ፣ በአልባሳት፣ በህክምናና በተለያዩ አገልግሎቶች ከኪስ ገንዘቡ በማዋጣት የሚረዳ የሚመሠገን ሠራዊት ነው ብለዋል፡፡

በዝግጅቱ ላይ የተገኙት የኤዩሶም ቺፍ ኦፍ ስታፍ ሜጀር ጀኔራል ክንዱ ገዙ የደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ ህዝብና መንግስት ላዘጋጃችሁት ደማቅ አቀባበልና ሽኝት ስነ-ስርዓት በኢትዮጵያ መከላከያሠራዊትና ኤዩሶም ስም ምስጋና አቅርበዋል።

ለሠራዊታችንና ለሴክተሩ አመራሮች ያላችሁ ክብር ታላቅ እንደሆነ መረዳታቸውን የገለፁት ጄኔራል መኮንኑ ይህ ታላቅ ክብር ዛሬ የተጀመረ ሳይሆን የደቡብ ምዕራብ ሱማሊያ ህዝብና መንግስት ትላንት በአስቸጋሪ ወቅትም በአደባባይ ወጥቶ ኢትዮጵያዊያን የከፈሉትን ዋጋ እውቅና የሰጠን ህዝብና መንግስት ነው ብለዋል፡ቀጣይም ያለንን ግንኙነት አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡

ዘጋቢ ሰመረ እሸቱ

ፎቶግራፍ አይናለም ተክለፃዲቅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

http://localhost/defensenew

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ