የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አደረጉ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 07 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እ.ኤ.አ ከኤፕሪል 13 እስከ 16 ቀን 2025 በሩዋንዳ የስራ ጉብኝት አድርገዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ መከላከያ ሠራዊት ኤታማዦር ሹም ጄነራል ሙባረክ ሙጋንጋ በክብር ዘብ የታጀበ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በሁለቱ ሀገራት መከላከያ መካከል የሁለትዮሽ የጋራ ውይይት ተካሂዷል።

በሁለትዮሽ የጋራ ውይይት ማጠቃለያ ላይ የሩዋንዳ መከላከያ ሠራዊት ኢታማዦር ሹም ጄኔራል  ሙባረክ ሙጋንጋ እ.ኤ.አ. በመጋቢት ወር 2025 በኢትዮጵያ ባደረጉት የስራ ጉብኝት ወቅት በሁለቱ አገሮች መከላከያ መካከል በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ቀጣይ ትግበራ እና አፈፃፀም አቅጣጫ የሚያመለክት የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል።

ጉብኝቱ የረጅም ጊዜ የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከር ትልቅ እንድምታ ያለው ሲሆን ሁለቱ አገራት በመከላከያ እና ሌሎች ተያያዥ ዘርፎች ላይ በአዳዲስ የትብብር መስኮች ለመሥራት እና የቀጠናውን ሰላም እና ደህንነትን ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያመላክት ነው።

ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በጉብኝታቸው ከሩዋንዳ ፕሬዝዳንት ከክቡር ፖል ካጋሜ ጋር በሁለቱ ሀገራት መከላከያ መኖር ስላለበት ግንኙነትና ትብብር በተመለከተ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፤ እንዲሁም ከሩዋንዳው መከላከያ ሚኒስትር ጁቬናል ማሪዛሙንዳ ጋርም ተነጋግረዋል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ