የውጭ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን አቅም የሌላትና ደካማ ሀገር ለማድረግ ከመስራት አይቆጠቡም   ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም

የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ተገኝተው ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በየአቅጣጫው ነፍጥ እያነሱ ህዝባችንን ሰላም የሚነሱና ልማት የሚያደናቅፉ የሀገር ውስጥ ፅንፈኞች፣ የተፈጥሮ ሀብታችንን እንዳናለማና ጠንካራ ኢትዮጵያ እንዳትኖር የሚፈልጉ የውጭ ጠላቶቻችን ተላላኪና ጉዳይ አስፈፃሚ ባንዳ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ በየጊዜው በሚፈጠሩ ሀገር ወዳድ አርበኞቿ ፀንታ የቆመች ናት ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣ የአርበኞቻችንን ያክል ቁጥር ባይኖራቸውም የውስጥ ባንዳም ያልተለያት ሀገርም ናት ብለዋል።

አሁንም አገርን ለመበታተን እየተፍጨረጨሩ ያሉ የውጭ ተላላኪና ጉዳይ አስፈፃሚ ባንዳዎችን በመደምሰስ የሀገርን አንድነት ያስቀጠለው ሠራዊታችን የዚህ ዘመን አርበኛ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የውጭ ጠላቶቻችን ምንጊዜም የማይተኙልን በመሆናቸው፣ ሠራዊታችንን ጠንካራ፣ አስተማማኝና ግዳጁን በብቃት መፈፀም የሚችል አድርገን ገንብተነዋል ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዚህ ሠራዊት ሀገርም እኔም እንኮራለን፣ እናንተም ክብር ይገባችኋል ብለዋል።

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ