በክልሉ የተገኘው ሠላም የሠራዊታችን ክቡር መስዋዕትነት ውጤት ነው።

ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

በአማራ ክልል የተገኘው ሠላም የሠራዊታችን ክቡር መስዋዕትነት ውጤት ነው ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ።

ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በሰሜን ጎንደር ዞን ከደባርቅ ወረዳ አስተዳደር የፀጥታ አካላት ጋር በዞኑ አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታ ላይ ውይይት ባደረጉበት ወቅት  ሠራዊታችን በማይበገረው የዓላማ ፅናቱ እንዲሁም  ጀግንነቱ  ክልሉን ከፅንፈኛው መፈንጪያነት ወደ አስተማማኝ ሠላምና ልማት እንዲመለስ አድርጓል ብለዋል።

ፅንፈኛው ኃይል ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስና ስልጣንን ኢ-ህገ መንግስታዊ በሆነ መንገድ ለመያዝ በታሪካዊ ጠላቶቻችን እየተነዳ ያደረገው የቀቢፀ ተስፋ ሙከራ ከባድ ዋጋ አስከፍሎታልም ብለዋል ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ።

እኛ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስና ስልጣን በአቋራጭ ለመያዝ የሚመጡ ኃይሎችን ስርዓት እናስይዛለን እያደርግን ያለንውም ይሄንኑ ነው ያሉት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ዋጋ የከፈልንበትን ሠላም ማፅናትና በቁርጠኝነት መስራት ከአስተዳደር  እንዲሁም ከፀጥታ አካለቱ የሚጠበቅ ቁልፍ ተግባር ስለመሆኑም አሳስበዋል።

በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠልና የአካባቢውን ሠላም መጠበቅ  እንዲሁም ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ ከሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባም አቅጣጫ አመላክተዋል።

የዞኑ የፀጥታ ኃላፊዎችም  ሚሊሺያ፣ ሠላም አስከባሪውና መደበኛ ፖሊስ ራሱን አደራጅቶ የክልሉን ብሎም የዞኑን ሠላም ለመጠበቅና ለማፅናት በትኩረት እየተሰራ ስመሆኑንም ተናግረዋል።

የአካባቢው ማህበረሰብ የፅንፈኛውን አድራጎት ተረድቷልም ተገንዝቧልም ያሉት የውይይቱ ተሳታፊዎች አሁንም ሠላሙን ለማፅናት ራሱን አደራጅቶ ስለ ሠላም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው ብለዋል። ዘጋቢ አንዷለም ከፍያለው ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

http://localhost/defensenew

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።