ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሃመድ እና በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ የመከላከያ ሠላም ማስከበር ማዕከልን ጎበኙ፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሃመድ እና በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ በመከላከያ ሠላም ማስከበር ማዕከል የአለም አቀፍ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አሁናዊ የስራ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።

ጉብኝቱ በፈረንሳይ መንግስት የሚሰጡ አጫጭር ስልጠናዎች በሠላም ማስከበር ተሳትፎ ላይ ያላቸውን አዎንታዊ ገፅታ ለመመልከት እና ቀጣይ በሚሰጡ ስልጠናዎች በጋራ ለመስራትና ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ  ጉብኝቱ የሁለቱን ሀገራት ሕዝብና መንግስት የረጅም ጊዜ ወዳጅነት ለማጠናከር እንደሚረዳ ገልፀው ቀጣይ በሚሰጡ ስልጠናዎች ከማሰልጠኛ ኢንስቲትዩቱ ጋር በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
      
የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሃመድ በበኩላቸው የፈረንሳይ መንግስት የሚሠጠው አጫጭር ስልጠና አለም አቀፍ የሠላም ማስከበር ግዳጃችንን በተሻለ መንገድ እንድንፈፅም እገዛ የሚያደርግ ነውና ለቀጣይም የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡

የመከላከያ ሠላም ማስከበር ማዕከል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አዳምነሀ መንግስቴ የፈረንሳይ መንግስት እያደረገ ሥላለው ድጋፍ በመከላከያ ሠላም ማስከበር ማዕከል ስም አመሥግነዋል፡፡

ዘጋቢ ተፈራ ጥላዬ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
http://localhost/defensenew/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።