የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል ስኬታማ የግዳጅ አፈፃፀም ማስመዝገቡ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል የፀረ-ሰላም ሀይሎችን እንቅስቃሴ በመግታት መስዋዕትነት ከፍሎ ሀገርን ከመፍረስ የታደገ ክፍል ነው ሲሉ ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ተናገሩ።

ክፍሉ በውጊያ ውስጥ ሁኔታን የሚቀይር ለሌሎች ክፍሎች የውጊያ እንቅስቃሴን የሚያመቻች ጀግና እና አርአያ የሆነ ክፍል ነው ብለዋል።

የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል በአጭር ጊዜ በመደራጀት በርካታ የሀገር መሪዎችን እና ዲፕሎማቶችን ደህንነት በተሟላ መንገድ የመጠበቅ ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ መፈፀሙን ገልፀዋል።

ጀኔራል ጌታቸው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል አባላት ዘንድሮ የተመዘገበውን ውጤት ቀጣይም አስጠብቃችሁ በተሻለ ውጤት እንደምታስቀጥሉ እምነቴ የፀና ነው ብለዋል።

በአመቱ ከጓድ መሪ ጀምሮ እስከ ሻለቃ አመራር ድረስ የተሰጠው ስልጠና እንዲሁም በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የተሰጡ የተለያዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎች ክፍሉ የተሻለ የማድረግ አቅም እንዲኖረው ያሥቻለ መሆኑን ገልፀዋል።

የጥበቃ ሃይሉ የተለያዩ ሀገር ዲፕሎማቶችን በክብር በመቀበልና በመሸኘት የሀገርን ገፅታ በመገንባትና መሪዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ የተለያዩ አለማቀፋዊ እና አህጉራዊ ስብሰባዎች በስኬት እንዲጠናቀቁ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በአስተማማኝ ሁኔታ የቆመለትን አላማ እየፈፀመ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በመዝገቡ ያረጋል

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።