የሳንባ ምች ምንነት፣ መንስዔና ህክምና

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም

የሳንባ ምች በባክቴሪያ፣ በቫይረስ ወይም በፈንገስ ምክንያት የሚመጣ የአንዱ ወይም የሁለቱም ሳንባ ኢንፌክሽን ነው።

ማንኛውም ሰው በሳንባ ምች ሊጠቃ የሚችል ቢሆንም በከፍተኛ ሁኔታ ለበሸታው ተጋላጭ የሆኑት ዕድሜያቸው 65 እና ከዚያ በላይ የሆኑ አዋቂዎች፣ ከ2 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት፣ የጤና እክል ያለባቸው ሰዎች እና የሚያጨሱ ሰዎች ናቸው ተብሏል፡፡

በባክቴሪያ የሚመጣ የሳንባ ምች ምልክቶች፡- የከንፈር እና ጥፍር ሰማያዊ መሆን፣ ግራ መጋባት ወይም ድብርት (በተለይም በዕድሜ የገፉ ሰዎች ላይ)፣ (አረንጓዴ፣ ቢጫ ወይም ደም ያለበት) ፈሳሽ ያለው ሳል፣ ትኩሳት፣ ከባድ ላብ፣ የምግብ ፍላጎት ማጣት፣ ከፍተኛ ድካም፣ ቶሎ ቶሎ መተንፈስ፣ ፈጣን የልብ ምት፣ መንቀጥቀጥ ወይም ብርድ ብርድ ማለት፣ በረጅሙ መተንፈስ ወይም ማሳል፣ የደረት ህመም (ውጋት)፣ በተለይም በእንቅስቃሴ ወቅት እየተባባሰ የሚሄድ የትንፋሽ ማጠር አና ሌሎችም

በቫይረስ የሚመጣ የሳንባ ምች ምልክቶች፡- ራስ ምታት፣ የትንፋሽ እጥረት፣ የጡንቻ ህመም፣ ድካም እና ከባድ ሳል ይጠቀሳሉ፡፡

ብዙውን ጊዜ ህክምናው የሚደረገው በቅርብ ጊዜ ባለዎት የጤና ሁኔታ ሲሆን ፥ እንደ ቀዶ ጥገና፣ ጉንፋን እና መሰል ህመምን መሰረት በማድረግ ነውም ይላሉ የሕክምና ባለሙያዎች።

የሳንባ ምች ካለብዎ ሃኪም ያዘዘልዎትን መድሃኒት ሳያቋርጡ መውሰድ፣ በአግባቡ ምግብ መመገብ፣ ፈሳሽ በበቂ መውሰድ፣ እረፍት ማድረግ፣ ራስ ምታቱን መቆጣጠር እንዲሁም የኦክስጅን ህክምና መውሰድ በሽታው እንዳይባባስና ሌሎች ተጓዳኝ የጤና እክሎችን እንዳያስከትልብዎ ይረዳል፡፡

ጉንፋን የተለመደ የሳንባ ምች መንስኤ እንደሆነ የሚነሳ ሲሆን፥ ራስን ከጉንፋንና መሰል በሸታዎች መከላከል ይገባል፡፡ ተጋላጭነቱ ከዚህ ባስ ሲልም ማለትም ህጻናትና በእድሜ የገፉ ሰዎች የጉንፋን ወይም የሳንባ ምች ክትባት እንዲወስዱ ማድረግም እንደመፍትሄ ይወሰዳል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።