የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልን ጎበኙ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና አሠጣጥ ሂደቱን ተመልክተዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የሪፈራል ሆስፒታሉን የእንግዳ ማረፊያም መርቀዋል። የእንግዳ ማረፊያው ሁሉንም ዓይነት የእንግዳ መቀበያ መሥፈርት ያሟላ 26 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ነው።

የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና አሠጣጥ ሂደቱን የተመለከቱት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ሆስፒታሉ በህክምና መሣሪያዎች ቴክኖሎጅና በሙያተኛ ዘመናዊነትን በተከተለ አግባብ ዘምኖ የሪፈራል ሆስፒታል መሆን እንዲችል መከላከያ ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ ማድረጉን ገልፀዋል።

በአለማችን በጦር መሣሪያ፣ በህክምና መገልገያ መሣሪያ፣ በኢንዱስትሪ እና በሌሎች የቴክኖሎጅ ዘርፎች ሞዴል የሚሆኑ ሙያተኞች የሚፈልቁት ከውትድርናው ቤት ነው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ኢትዮጵያ በየጊዜው ሲገጥማት በነበረው ጦርነት ምክንያት ሞዴል ሳንሆን መቆየታችንን ገልፀው አሁን ላይ ግን በሁሉም ዘርፍ ዘመናዊነትን በተከተለ አግባብ ከቴክኖሎጅው ጋር መላመድና አብሮ ማደግ ይኖርብናል ብለዋል።

ሪፈራል ሆስፒታሉን በማዘመን ወደ ውጪ የሚሄዱ ታካሚዎች እዚሁ እንዲታከሙ የማድረጉ ጥረት ትልቅ ተስፋ ሰጪ በሆነ መንግድ ስኬታማ ሆኗል ለዚህም የ87 የሠራዊት አባላት የዳሌ አጥንት ቅየራ ሥራ በውጤት መሣካት ዋናው ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።

የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የሆስፒታሉ ፅዳትና ውበት እጅግ በተለዬ መንገድ ሳቢ ለሥራ ምቹነት የሚፈጥር ሞዴል በሆነ አግባብ መሠራቱን አድንቀው የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ኃላፊን ጨምሮ የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አመራሮች ላደረጉት ያልተቆጠበ የሥራ ተነሳሽነት ምስጋና አቅርበዋል።

በጉብኝቱ ላይ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላን ጨምሮ ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና ጄኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ ውብሸት ቸኮል

ፎቶግራፍ ተሠማ ኡርጌሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

http://localhost/defensenew

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 

http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ

http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።