ጦርነትን ለማሸነፍ የስነ-ልቦና ዝግጁነት ወሳኝ መሆኑን ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ተናገሩ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

ጦርነትን ለማሸነፍ የስነ-ልቦና ዝግጁነት ወሳኝ ነው ሲሉ የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ተናገሩ።

ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ በሰሜን ምዕራብ ዕዝ  ማሰልጠኛ ማዕከል ተገኝተው በስልጠና ላይ ለሚገኙ የሬጅመንትና ሻምበል አመራሮች በሠራዊት የስነ-ልቦና ግንባታ  ዙሪያ ትምህርት በሰጡበት ዕለት የተቋማችንን የፕሮፌሽናል ሠራዊት ግንባታ ስኬታማ ለማድረግ ደስተኛና በራሱ የሚተማመን፤ ስነ-ልቦናና አካላዊ ብቃቱ የተረጋገጠ ሁለንተናዊ አቅም ያለው አመራርና ሠራዊት ማዘጋጀት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

ሌተናል ጄንራል ጥጋቡ ይልማ የሠራዊቱን ስነ-ልቦና ለማረጋገጥ በስልጠናና በዕውቀት ክህሎትን በማዳበር ከዘመኑ ጋር የሚዘመን በጠንካራ ስነ-ልቦና የምንመራው የጦር ክፍል ማሰልጠን፣መገንባትና ማብቃት  ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የምንመራው ሠራዊት አቅሙ እንዲጎለበትና የሚሰጠውን ግዳጅ በድል እንዲወጣ አመራሩ ተከታታይነት ያለው የስነ-ልቦና ግንባታ ስራዎችን መስራት  ይጠበቅበታል ብለዋል።

የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ  ፅንፈኛውን ኃይል በመደምሰስ በመስዋዕትነታችን ያረጋገጥነውን ሠላም የበለጠ ለማፅናት አቅማችንን ማጎልበትና ተልዕኳችንን በላቀ ብቃት ለመወጣት የበለጠ መዘጋጀት እንደሚገባም አሳስበዋል።

ዘጋቢ ይሁን አሻግሬ
ፎቶግራፍ እያሱ ጃርሶ 

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
http://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
http://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
http://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ስፖርት

j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ
m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።