ተልዕኳችንን በማሳካት የኢትዮጵያን ልማት እና የህዝባችንን ሰላም እናረጋግጣለን     ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት

ተልዕኳችንን በማሳካት የኢትዮጵያን ልዕልና እና የህዝባችንን ሰላም እናረጋግጣለን ሲሉ የምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት ተናግረዋል።

አዛዡ ምዕራብ ዕዝ በተለያዩ ጊዜያት ፀረ-ሠላም ኃይሎች ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ለመበተን የጠነሰሱትን ሴራ በጀግንነት አምክኗል፤ አሁንም በቁርጠኝነት በማምከን ላይ ይገኛል ብለዋል።

የማህበራዊ ሚዲያ አርበኞች ኢትዮጵያ ልትፈርስ ነው፤ አበቃላት ይላሉ፤ ነገር ግን ኢትዮጵያ ወደየት እየተጓዘች እንደሆነ እያወቁ እንዲህ አብዝተው የሚጮሁት ከባንዳነት ተልዕኮ የሚያገኙት ጉርሻ በልጦባቸው መሆኑን እንረዳለን ያሉት ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት የሀገራችን ህዝቦች እውነታው የቱ ጋር እንዳለ በውል ተረድተዋል፤ የኢትዮጵያ ትንሳኤ አይቀሬ መሆኑን ያሳየው የህዳሴ ግድባችን ታላቅ ምስክር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ የይቻላል መንፈስ ከፍታና ዳግማዊ አድዋ ስኬት ደግሞ በዋዛ የተገኘ ድል ሳይሆን ለኢትዮጵያ ልዕልና በፍቃደኝነት መተኪያ የሌላትን ህይወታቸውን መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተው በተግባር ማረጋገጥ የቻሉ ውድ ጀግኖች የሠራዊት አባላትና የድላችን መሠረት እንዲሁም ፅኑ ደጀን የሆኑ አርበኛ ኢትዮጵያዊያን በመኖራቸው እንደሆነም አሥረድተዋል።

የኢትዮጵያ የትንሳኤ ጉዞ ገና በጣም ረጅም ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል መሠለ መሰረት፤ የሀገራችን ሉዓላዊነትና የህዝባችን ሠላም የህብር ጥረት ድምር ውጤት እንደመሆኑ መጠን ሁሉም ዜጋ ለሠላምና ልማት መረባረብ አለበት ብለዋል።

ምዕራብ ዕዝ በርካት ድሎችን ያሰመዘገበ መሆኑን የጠቆሙት ዋና አዛዡ አሁንም ተልዕኳችንን እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በላቀ ጀግንነት በመወጣት የበለፀገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማሻገር መላው የሠራዊታችን አመራርና አባላት ይበልጥ ቀን ከሌት መትጋት ይጠበቅብናል ሲሉ አሥረድተዋል።

ዘገቢ ፍፁም ከተማ
ፎቶ ግራፍ  አከለ አባተ

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ