ሠንደቅ ዓላማ እና ሠራዊት ከቃል እስከ ህይወት መስዋዕትነት የተገመደ ትስስር አላቸው       ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም

“ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሃሳብ ብሄራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን በመከላከያ ሚኒስቴር ጠቅላይ መምሪያ ተከብሯል።

በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ከፍታ  ከሀገራዊ ክብርና ማንነት ጋር በቀጥታ የተቆራኘ በመሆኑ የሀገር ክብር የሚረጋገጠው ደግሞ ብሔራዊ ጥቅሞቻችን በተሟላ መንገድ ሲጠበቅ ነው ብለዋል።

ታሪካዊ ጠላቶቻችን በቻሉት ሁሉ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም በመፃረር በእጅ አዙር የውስጥ ባንዳዎችን በማደራጀት እና በመደገፍ ሲውተረተሩ ይስተዋላሉ ያሉት ጀኔራል መኮንኑ ተላላኪ ባንዳዎችም የተሰጣቸውን አጀንዳና እኩይ አላማ ለማስፈፀም ከዚህም ከዚያም በትጥቅ እንቅስቃሴ ቢያደርጉም ከንቱ ምኞታቸው መክኗል ሲሉ ገልፀዋል።

ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና ሀገራችን ኢትዮጵያም በዚህ ትውልድ ዘመን ከህዝቦቿ እና ከሠራዊቷ ጋር ሆና ወደ ከፍታ ዘመን ትሸጋገራለች ነው ያሉት።

ሠንደቅ ዓላማ እና ሠራዊታችን ከቃል እስከ ህይወት መስዋዕትነት የተገመደ ትስስር አላቸው ያሉት ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና የሀገራችን መንግስትና ህዝብ ያነገቡትን ሀገራዊ ጥቅም የማረጋገጥ አጀንዳ እውን ለማድረግ እኛ የሠራዊት አመራሮችና አባላት የተጣለብንን ሀላፊነት በላቀ ደረጃ በመፈፀም በሠንደቅ ዓላማችን ስር የገባነውን ቃል በተግባር ላይ ልናውል ይገባልም ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወቅታዊ አጀንዳ

p
የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ በማንኛውም አይነት ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ ተልዕኮውን እየተወጣ ነው፡፡   ብርጋዴር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ
m
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረመ።
j
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል፦    ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ

ስፖርት

p
የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ በማንኛውም አይነት ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ ተልዕኮውን እየተወጣ ነው፡፡   ብርጋዴር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ
m
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረመ።
j
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል፦    ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።