የኢፌዴሪ የስራና ክህሎት ሚንስቴር ሚኒስትር ክብርት ሙፈሪያት ከሚል፤ የመከላከያ ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ አህመድ እና የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጀኔራል ይመር መኮንን አንጋፋውን የሜጄር ጄኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጎብኝተዋል።
ኮሌጁን ተዘዋውረው የጎበኙት ክብርት ሙፈሪያት ከሚል ኮሌጁን የልዕቀት ማዕከል ከማድረግ ባለፈ በሙከራ ላይ ያሉ ፈጠራዎችን ወደ ምርት በመለወጥ ለሀገርና ለተቋም የሚሰጡት ዕምቅ አቅም መኖሩን መረዳታቸውን ገልፀዋል።

ለተቋምና ለሀገር አንጋፋና ታሪካዊ የሆነው ኮሌጁን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በጋራ መስራት እንደሚገባ የገለፁት ሚኒስትሯ ለዚህም ተቋማቸው በስልጠና ፣ በሰው ሀይል ግንባታና በቴክኖሎጂ የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
ኮሌጁን ከመከላከያ ኢንተርፕርነርሺፕና ኢኖቬሽን ማዕከል ጋር በማቀናጀት ለተቋሙና ለሰራዊቱ ጥቅም ለመስጠት ምቹ መደላደል መሆኑንም ጠቁመዋል።
ኮሌጁ ያለውን አሻራ በመጠቀም ለወደፊቱ የሚዘጋጅ ወታደራዊ የቴክኒክ ኮሌጅም ለማድረግ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባም ተናግረዋል።
በጉብኝቱ ላይ በኮሌጁ መምህራንና ተማሪዎች የተሰሩ በርካታ የፈጠራ ምርቶች የተጎበኙ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የኮሌጁ አዛዥ ብርጋዲየር ጀነራል አበበ ዋቅቶላን ጨምሮ የኮሌጁ መምህራንና ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ገነት አወቀ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official





