ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል ለወራት ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች በዛሬው ዕለት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ የመሠረታዊ ውትድርናን እና የመሠረታዊ ኮማንዶ ምልመላ መስፈርቶችን ያሟሉ ናቸው።

በምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ የውትድርና ሙያ የጀግንነት ስብዕና የተላበሰ ማንነትን የሚፈልግ ከመሆኑም በላይ ፈታኝ ለሆኑ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩ በፅናት መቆምን ይጠይቃል ብለዋል።

ይህ ሲሆን በሚያልፍ ህይወት የማያልፍ ታሪክን በመፃፍ በዜጎች ልብ ውስጥ በትውልድ ቅብብሎሽ ለዘለዓለም መኖር እንደሚቻልም ጀነራል መኮንኑ ገልፀዋል።

የመሠረታዊ ውትድርናን አጠናቀው የተመረቁት ወታደሮች በቀጣይ ከኮማንዶ ከአየር ወለድ ከልዩ ኃይልና ፀረ-ሽብር እንዲሁም ከሪፐብሊኩ የጥበቃ ኃይል ጋር ለመቀላቀል የሚያስችላቸውን ስልጠና በብቃት እንዲወጡም አሳስበዋል።

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝና የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል አመራርና አባላት ኢትዮጵያ አስቸጋሪ ሁኔታዎች በገጠሟት ጊዜ ሁሉ አለኝታነታቸውን በተግባር  ያረጋገጡ የቁርጥ ቀን ልጆች መሆናቸውንም ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ገልፀዋል።

ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ጠንካራ የአካል ብቃት፣ የተኩስና የተለያዩ የውጊያ ስልቶችን በቀንና በሌሊት የተማሩና በልምምድ ያዳበሩ ከመሆኑም በላይ የስነ-ልቦናና የጤና ትምህርትን የቀሰሙ መሆናቸውን  የገለፁት ደግሞ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል አዛዥ ብርጋዲየር ጄነራል ቦጃ አጋ ናቸው።

ማሠልጠኛ ማዕከሉ የቅበላ አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉን የገለፁት ብርጋዲየር ጄነራል ቦጃ አጋ የሥልጠና መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት ተችሏልም ብለዋል።

ተመራቂዎች በስልጠና ቆይታቸው አሠልጣኞችና አመራሮች እነሱን ለማብቃት ላደረጉት ሁለንተናዊ ጥረት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይ ለሚጠብቃቸው የመሠረታዊ ኮማንዶ ስልጠና ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ