የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ በማንኛውም አይነት ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ ተልዕኮውን እየተወጣ ነው፡፡   ብርጋዴር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ

በደቡብ ሱዳን ደቡባዊ ሴክተር ተሰማርቶ የሚገኘው የ22ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ የተሰጠውን ተልዕኮ በላቀ ብቃት በመወጣት ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡

የኢትዮጵያ ሠራዊት በማንኛውም ዓይነት ተግዳሮትና ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ የሚሰጠውን ተልዕኮ በብቃት መፈጸም የሚችል ጀግና መሆኑን በደቡብ ሱዳን የደቡብ ሴክተር ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ ገለፁ።

ዋና አዛዡ በቀጠናው ተሰማርቶ ለሚገኘው የ22ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አሥከባሪ ሻለቃ አመራር እና አባላት በቀጠናው በተሰማሩ አጭር ጊዜ ውስጥ ላስመዘገቡት እና እያስመዘገቡ ላለው ውጤታማ የተልዕኮ አፈጻጸም ምስጋናና ዕውቅና በመስጠት የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ሠራዊት ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎችን በስኬት የመወጣት የረጅም ጊዜ ታሪክ እና ልምድ ያለው መሆኑን ያወሱት ጄነራል መኮንኑ አሁን ላይ የሻለቃው አባላት በደቡብ ሱዳን እያሳዩት ያለው ጀግንነትና የዲሲፕሊን ልዕልና የአገሪቱን መልካም ስም ይበልጥ የሚያስጠራ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ የታየው ቁርጠኝነት ለአካባቢው ማህበረሰብ አስተማማኝ ዋስትና የሚሰጥ እና ለቀጣይ የሰላም ጥረቶች ትልቅ መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑን በመገንዘብ ሠላም አስከባሪዎች የተጣለባቸውን አለም አቀፋዊ ኃላፊነት በታማኝነትና በጀግንነት ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የሞተራይዝድ ሻለቃው በቀጠናው በተሰማራ በአጭር ጊዜ ውስጥ እያስመዘገበ ላለው ውጤታማ የተልዕኮ አፈጻጸም ያላቸውን ከፍተኛ አድናቆት በመግለጽ ለሻለቃው አመራር እና አባላት የዕውቅና ሰርተፊኬት አበርክተዋል።

ዘጋቢ ቢኒያም ማሞ
ፎቶ ግራፍ ገዛኸኝ ፀጋዬ

ወቅታዊ አጀንዳ

p
የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ በማንኛውም አይነት ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ ተልዕኮውን እየተወጣ ነው፡፡   ብርጋዴር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ
m
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረመ።
j
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል፦    ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ

ስፖርት

p
የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ በማንኛውም አይነት ፈታኝ ሁኔታ ሳይረታ ተልዕኮውን እየተወጣ ነው፡፡   ብርጋዴር ጄኔራል ሺሺር ባራድዋጅ
m
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ከሪፖርታጅ ፕሮፐርቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረመ።
j
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ያስመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል፦    ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
j
ኢትዮጵያ በየዘመኑ በታሪካዊ ጠላቶች እና በውስጥ ባንዳዎች ብትፈተንም፤ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ፍላጎታቸውን እያከሸፈው ይገኛል።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
m
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ71ኛ መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመርቋል። 
af
የሎጂስቲክስና የኮሙኒዩኬሽን አቅም የሀገራትን ዕድገትና ተፅዕኖ የሚወስን መሠረታዊ ኃይል ነው።       ዶክተር አለሙ ስሜ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።