የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም
የብርሸለቆ መሠረታዊ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በዛሬው ዕለት 41ኛ ዙር መሰረታዊ ወታደሮችን አሥመርቋል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ በክብር እንግድነት በመገኘት ሰልጣኞችን የመረቁት የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሃመድ ተሰማ ፣ የመከላከያ ሃይልን በሰው ሃይል ልማት ከዘመኑ ወታደራዊና ቴክኖሎጂያዊ ትጥቆች በመደገፍ ውጤታማ ግዳጆችን እንዲወጣ ለማስቻል ዘርፈ ብዙ ተግባራት መሠራቱን ገልፀዋል።
ውትድርና ሙያ ከሌሎች ሙያ ልዩ የሚያደርገው አንዱና ዋነኛው መንገድ ክብርና ውድ ህይወቱን ሰውቶ አገርን ማፅናት፣ ህዝብን ማገልገል የሚጠይቅ ሙያ መሆኑ እንደሆነ የገለፁት አዛዡ ይህን ሙያ በጥብቅ ዲስፕሊን
ለመፈጸም ደግሞ መስልጠን ሙያው የሚጠይቀውን እውቀት ብቃት ችሎታ መፍጠርና በስነ-ልቦና መዘጋጀት የግድ መሆኑን አሥረድተዋል።
የ41ኛ ዙር ተመራቂ መሠረታዊ ወታደሮች በውትድርና ሙያ አገራችሁንና ህዝባችሁን በፍፁም ታማኝነት ለማገልገል ፈቅዳችሁ፣ ሰልጥናችሁ ወደ ተቋሙ የተቀላቀላችሁ የጀግና ህዝብ ልጆች ስለሆናችሁ ልትኮሩ ይገባል ብለዋል፡፡
በማስልጠኛ ቆይታችሁ ያገኛችሁትን መነሻ አቅም በመጠቀም በምትመደቡበት አሃድ ከነባሩ ሠራዊት የምታገኙትን ልምድና ተሞክሮ ጨምራችሁ በየጊዜው አቅማችሁንና ብቃታችሁን በማሳደግ የሚሰጣችሁን ህገ – መንግስታዊ ተልዕኮ ሠራዊቱ የተገነባባቸውን እሴቶችና ህዝባዊ ባህሪን ተላብሳችሁ በጀግንነት፣ በታዛዥነትና በፅኑ ዲስፕሊን ልትወጡ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
በአወል መሃመድ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ





