የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም

በትጥቅም ሆነ በትጥቅ ግብዓቶች የመከላከያ ሠራዊቱን የዝግጁነት ደረጃ ለማሣደግ በውጤት እየሠራን ነው ሲሉ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም ተናገሩ

ቆየት በሚል ስያሜው የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በሚል ሲጠራ የነበረው አሁን ላይ ተቋሙ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በደንብ ቁጥር 567/2017 በመፅደቁ የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ በመባል አድማሱን በማስፋት በርካታ ኢንዱስትሪዎችን አካቷል።

ለመከላከያ ሠራዊት የተለያዩ ትጥቆችን እና የትጥቅ ግብዓት ምርቶችን በማምረት እና የተለያዩ የኮሜርሻል ምርቶችን በማምረት እንደ ተቋም ብሎም እንደ ሀገር ብቸኛው ተቋም ከመሆኑ አንፃር ትልቅ የሃይል አቅም በመሆን ዘርፈ ብዙ በቴክኖሎጂ የታገዙ ተግባራትን እያከናዎነ እንደሚገኝ የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያም ገልፀዋል።

መንግስትና ተቋሙ ለመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠታቸው በሪፎርሙ አዳዲስ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም የምርትና ምርታማነትን በማምረት የሠራዊቱን የዝግጁነት አቅም በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

የመከላከያ ኢንጂነሪግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሃብት አስተዳደር ዘርፍ ኮሎኔል ዩሃንስ ትኬሳ በበኩላቸው እየተመዘገበ ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለተቋሙ ብሎም ለሀገራችን ከፍታ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

የመከላከያን ፍላጎት ለማሟላት የኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፑ አመራርና ሠራተኛ በአንድ እስትንፋስ ምርትና ምርታማነትን በማሣደጉ ረገድ ሥራቸውን በአግባቡ በመፈፀም ሀገራዊ ተልዕኳቸውን በስኬት የመወጣቱን ሂደት አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ኮሎኔል ዩሃንስ ተናግረዋል።

በመስከረም ብርሃኔ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

ወቅታዊ አጀንዳ

as1
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን የመከላከያ ሚኒስትሯ ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ።
as
ኢትዮጵያ እና ኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቢል ) በወታደራዊ መስኮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
s6
በአምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ የተፃፈው ''የፀረ-ሽምቅ ውጊያ ጥበብ'' መፅሐፍ ተመረቀ።
mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።

ስፖርት

as1
ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን የመከላከያ ሚኒስትሯ ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ።
as
ኢትዮጵያ እና ኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቢል ) በወታደራዊ መስኮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
s6
በአምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ የተፃፈው ''የፀረ-ሽምቅ ውጊያ ጥበብ'' መፅሐፍ ተመረቀ።
mf
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አካል መሆን እንዳለባት የፈረንሣይ የምድር ኃይል አዛዥ ጄነራል ፒየር ሺል ገለፁ።
ay3
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Y
ፈረንሣይ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ መስክ የበለጠ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን የፈረንሣይ ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል ፒየር ሺል ገለፁ።

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ