መከላከያ ሠራዊት የህዝብ ኩራት የሀገር ክብር !

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የምንጊዜም መነሻ እና መድረሻ መሠረቱ ኢትዮጵያ ነች፡፡ ኢትዮጵያን ከጠላት መጠበቅ፣ ዘወትር ለሠላሟ መሥራት፣ ለዕድገቷ መታተር ፣ለክብሯና ለነፃነቷ መታገል፣ ለህዝቦቿ አንድነትና ሠላም ዘብ መሆን ፣ብሄራዊ ጥቅሟን ማሥከበር ሁሌም የሚፈፅማቸው የየዕለት ተግባራቶቹ ናቸው።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሀገር ላይ እጃቸውን የሚሰነዝሩ የጥፋት ኃይሎችን በብቃት እየመከተ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን እያመከነ ሠላምና ልማትን እያሥቀጠለ የሚገኝ የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የህብረ ብሄር ቡቃያ ነው።

ለሀገሩ እና ለሠንደቅ ዓላማው ክብር ሲል ለተልዕኮው ቅድሚያ የሚሠጠው ሠራዊት በየትኛውም ጊዜ የተሠጠውን ተቋማዊና ሀገራዊ ተልዕኮ በድል የተወጣ ፣እየተወጣ የሚገኝ፣ ህዝባዊነቱን የሚያሥቀድም፣ በህዝቦች ልቦና የታተመ ሥለመሆኑ ሁሉንም ያግባባል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ተልዕኮ በሚፈፅምባቸው ቀጠናዎች ሁሉ የህዝብ ድጋፍ ያልተለየው ህብረተሠቡ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ አብሮነቱን የሚገልፅለት በመሆኑ ድልን እየተጎናፀፈ ሠላምና ልማትን እያሠፈነ የሚገኝ ተመራጭ የሠላምና የልማት ኃይል ነው።

ሠውን ለማኖር በሰዋዊ በጎነቱ እስከ ህይወት መስዋዕትነት የሚከፍል ፣ ልጅ ሚስት ቤተሰቡን ትቶ ሁሌም ለሀገር ሠላም ለተሠለፈው፤ የሀገሩን ክብር ለማሥጠበቅ ለሞት ለማያመነታው፣ ለነፃነት ታሪክ ሰሪ ታሪክ አሻጋሪ፣ የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም የሚያሥከብር ኃይል ነው። ታዲያ ለጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ልናደርግለት የምንችለው ጥቂት ነገር ምስጋና ማቅረብ አይደለምን ?

አዎ! በተሳሳተ አመለካከት እየተነሱ ሲተኩሱበት መሣሪያውን የሚዘቀዝቅ ህዝብ አክባሪ የሆነውን ሠራዊት ማክበር ታላቅነት ነው፣ የራሱን ስንቅ ለህዝብ የሚያድል የሀገር እና የህዝብ አለኝታ የአንድነታችን አርአያ የሆነውን ሠራዊት ማክበር፣ መደገፍ ፣ከጎኑ መቆም ሀገርን ከመውደድ ባሻገር መታደልም ነው።

የኢትዮጵያን አንድነት እያሥጠበቀ ሀገርን ለትውልድ እያሸጋገረ የሚገኘውን መከላከያ ሠራዊት ማክበር ክብር መሥጠት ማመስገን እና ሁሌም ከጎኑ መሠለፍ ተገቢም አማራጭም ነው።

ለዛም ነው መከላከያ ሠራዊቱን መውደድ መከላከያ ሠራዊቱን ማክበር ሀገርን መውደድ ሀገርን ማክበር ነው የምንለው።

በውብሸት ቸኮል

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

ወቅታዊ አጀንዳ

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ስፖርት

m
የኤሌክትሮኒክስ ዋርፌር የህልውና ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ በዘርፉ የሀገራችንን አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።    ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
hu
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አሰመረቀ።
shu
ውትድርና ጀግንነትን እና ስብዕናን ተላብሶ ሠው ሰራሽና የተፈጥሮ መሠናክሎች ሳይበገሩት በፅናት መቆምን ይጠይቃል፦       ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
SS1
ከተጣሉበት በማንሳት በራስ አቅም ተሻሽለው ወደ ሀይል የገቡት ትጥቆች የተቋሙን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራሉ።     ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
SSS
የሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋምና ለሀገር የሚሠጠውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
ASH
የውስጥ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀም ለተቋማዊና ሀገራዊ ጥቅም ማዋል ይገባል።  ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ

ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ለህገ መንግስቱ፣ ለሀገራችን መንግስትና ህዝቦች ፍፁም ታማኝ የሆነ፣ ጦርነትን የሚያቆም የልህቀትና የፍቅር ማዕከል የሆነ፣ በአስተማማኝ እና በብቃት በአገር አቀፍና በአለም አቀፍ ግዳጅ የሚያሳካ ዘመናዊ የመከላከያ ሰራዊት ማየት።

ማህበራዊ ሚዲያ