ኢትዮጵያ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊያን ለመፍታት በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኗን የመከላከያ ሚኒስትሯ ክብርት ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ገለፁ።
በአፍሪካ ሕብረት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአፍሪካ የመከላከያ መሪዎች ጉባዔ ተጠናቋል።ጉባኤው አህጉሪቱ እየተጋፈጠች ያለችውን የሽብርተኝነት፣ መፈንቅለ መንግሥት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ የእርስ በእርስ ግጭት፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ሌሎች የደኅንነት ቀውሶችን በተባበረ…